የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ለሲዳማ ህዝብ ታሪካዊ መልዕክት አስተላለፈ።

(ኦሮሚዲያ, 20 ሰኔ 2020) የኦሮሞ ነፃነት ግንባር(ኦነግ) ለመላው የሲዳማ ህዝብ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፈ።

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) የሲዳማ ብሔር የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ጥያቄ በሰላማዊ ትክክለኛና ህጋዊ በሆነ መልኩ እልባት ማግኘቱን አስመልክቶ ባስተላለፈዉ መልዕክት ስኬቱ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለዉ አዉስቷል።

“ይህ ስኬት የራስንዕ ዕድል በራስ የመወሰን መብቱን ለማስከበር ለዘመናት መራራ ትግል ሲያካሄድ ለኖረው የሲዳማ ሕዝብ ታላቅና ታሪካዊ ድል ነው።”

ኦነግ በመልዕክቱ እንደገለፀዉ የሲዳማ ህዝብ የዘመናት ጥያቄ ሆኖ የቆየው ራሱን በራስ የማስተዳደር እና በክልል የመደራጀት ህገ፡መንግስታዊ ጥያቄ ከረጅም ጊዜ ትግልና መስዋትነት በኋላ የተገኘ በመሆኑ ምሳሌነቱም አስተማሪና አበረታችም ነው።

ኦነግ በመልዕክቱ እንደገለፀዉ የሲዳማ ብሔር በመሪር ትግሉ የተጎናፀፈው ይህ ድል ልክ እንደ ሲዳማ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብታቸውን ለማስከበር በመታገል ላይ ለሚገኙ ሌሎች ሕዝቦችም መልካምና ተስፋ ሰጪ ዜናም ነው ።

የሲዳማ ህዝብ ታሪካዊ በክልል የመደራጀት ጥያቄው ዛሬ እውን ሆኖ በይፋ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መምጣቱ ትልቅ ድል መሆኑን ያወሰዉ ኦነግ “ለሲዳማ ብሔር እንኳን የትግልህ የድል ፍሬ እና የታጋዮች ልጆች መስዋዕትነት ዉጤት የሆነውን ይህን ታሪካዊ ደስታ ለማጣጣም በቃህ” በማለት መጪዉ ጊዜ የዘመናት ጥማት የሆኑት ነፃነት ሰላምና ዴሞክራሲ (ፍትሃዊ አስተዳደር) የሚረጋገጡበት እንዲሆን መልካም ምኞቱን ገልጿል።

የሲዳማ ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር ህገ፡መንግስታዊ ጥያቄው ምላሽ እንዲያገኝ ለረጅም ጊዜያት ያለመታከት ታግሏል።

የሰላም አምባሳደር የሆነው የኦሮሞ ህዝብ ከአጎራባች እና ሌሎች ኢትዮጵያዊያን ህዝቦች ጋር ያለው ኢኮኖሚያዊ ፣ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መስተጋብር እንዲጠናከር ከመቼውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ኦነግ በዚሁ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክቱ ገልጿል።

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰኔ 11 2012 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ፌዴረሽን አባል መንግስታት አንዱና አሥረኛዉ (10ኛዉ) ሆኖ በመዋቀር በይፋ የክልላዊ መንግስት ሥልጣኑን በመረከብ በይፋ የክልል ምስረታ ስልጣን ርክብክብ አድርጏል፡፡

የሲዳማ ህዝብ ህገ፡መንግስቱ ያጎናፀፈውን መብት በመጠቀምም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአካሄደው ህዝበ ውሳኔ መነሻ ይፋ በሆነው የድምጽ ውጤት መሠረት የራሱን ክልል ለማደራጀት የሚያስችል ድምጽ ማግኘቱ የሚታወስ ነው።

Advertisement

About advocacy4oromia

The aim of Advocacy for Oromia-A4O is to advocate for the people’s causes to bring about beneficial outcomes in which the people able to resolve to their issues and concerns to control over their lives. Advocacy for Oromia may provide information and advice in order to assist people to take action to resolve their own concerns. It is engaged in promoting and advancing causes of disadvantaged people to ensure that their voice is heard and responded to. The organisation also committed to assist the integration of people with refugee background in the Australian society through the provision of culturally-sensitive services.

Posted on June 20, 2020, in Uncategorized. Bookmark the permalink. Leave a comment.

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: