Daily Archives: October 24, 2025

Celebrating Irreecha: A Cultural Festival in Gambella

Gambella Community Celebrates Irreecha Festival with Grandeur at Malka Baro.

In a vibrant display of cultural pride and unity, the residents of the Gambella region came together at Malka Baro to celebrate the annual Irreecha festival in a grand and heartfelt ceremony.

The local community marked the occasion with deep reverence and joy, honoring the Oromo traditions of thanksgiving, peace, and renewal.

The celebration underscored the enduring strength and beauty of Oromo culture within Gambella’s diverse social fabric, serving as a powerful testament to shared heritage and community spirit.

የኢሬቻ በዓል በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች በዱባይ ከተማ በድምቀት ተከበረ፣

የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል “ኢሬቻ ለሀገር ማንሠራራት” በሚል መሪ ሃሳብ በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ዱባይ ከተማ በድምቀት ተከበረ፡፡

መርሃ -ግብሩ በአባ ገዳዎች እና ሃዳ-ሲንቄዎች መሪነት በፓርኩ ውስጥ በተዘጋጀው ቦታ ‘’በኢሬፋና’’ ሥነ-ሥርዓት ወይም ባህላዊ ምርቃት ተጀምሯል፡፡

በበዓሉ ላይ በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ቆንስላ ጄኔራል ጽ/ቤት ተጠባባቂ ጉዳይ ፈጻሚ አቶ አስመላሽ በቀለ በአገራችን ከሚከበሩ በዓላት ውስጥ የኢሬቻ በዓል የፍቅር፣ የሠላም፣ የወንድማማችነት እና የአብሮነት እሴት ያለው በዓል መሆኑን ገልጸው፣ ማህበረሰቡ በዚህ በዓል ላይ ያሳየውን አንድነት እና ድምቀት በሌሎች ውጭ አገራት ለሚገኙ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ተምሳሌት መሆኑ በመግለፅ በአገራችን እየተከናወኑ ባሉት አገራዊ የልማት ሥራዎች የሚያደርጉትን ተሳትፎ ይበልጥ እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል::

በመቀጠልም የአቡዳቢ ኤምባሲ ተወካይ አቶ ግርማ ደምሴ የዘንድሮውን ኢሬቻ ልዩ የሚያደርገው ከአገራችን የማንሰራራት ብስራት ጋር አብሮ እየተከበረ በመሆኑ ነው ብለው ለዚህም ማሳያው የዘመናት ቁጭታችን ውጤት የሆነው የሕዳሴ ግድብ ፕሮጄክት መመረቁ፣ የተፈጥሮ ጋዝ ምርት መጀመሩ እና ለአገራችን አርሶ አደሮች ትልቅ ግብዓት የሆነው የማዳበሪያ ፋብሪካ መጀመሩን አንስተዋል::

በተጨማሪም በዱባይ እና ሰሜን ኤምሬቶች የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የሥራ አመራር ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ኢድሪስ ቡንሱሩ የኢሬቻ በዓል በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች በጥቂት ሰዎች ተጀምሮ በየዓመቱ እያደገ መምጣቱን በመጥቀስ ዛሬ በሚታየው ደረጃ ላይ እንዲደርስ አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላትን አመስግነው የኮሚኒቲ ማህበሩ በፍቅር፣ በመቻቻል እና በመከባበር መርህ ኅብረተሰቡን በትጋት እያገለገለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በበዓሉ ላይ የኢሬቻ በዓል በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ዲፕሎማቶችና ሠራተኞች፣ የዱባይና አቡዳቢ የኢትዮጵያውያን ኮሚኒቲ ማህበር ሥራ አመራር ቦርድ አባላት፣ የተለያዩ የአገራችን ብሔር ብሔረሰቦች ተወካዮች፣ አባ-ገዳዎች፣ ሃዳ ሲንቄዎች እንዲሁም በርካታ ቁጥር ያለው ዜጎች ታድመዋል፡፡